በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
በቤቱ ሳለህ የእግዚአብሔርን ውለታ አለመርሳት
አዕምሮ ያላቸው ፍጡራን ሰዎች በእያንዳንዱ ኹኔታ ያሉትን አያሌ አማራጮችን የመመልክት ኃይል አላቸው፡፡ ፍጹም ኹኔታዎችን በማየት ፈንታ ተቃራኒ የኾኑትን ይፈልጋሉ፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ ግን እንዲህ በማለት ይናገራል "ወደ ሕይወት ልትገባ ብትወድ ትዕዛዛትን ጠብቅ" ይለናል ማቴ 19÷17፡፡ ነገር ግን በእግዚአብሔር ቤት ሳለህ ውለታውን ሳትረሳና ሳትወጣ ለመኖር ከፈለግኽ የሚከተሉትን ተጥቦች በጥልቀት መርምራቸው፡፡1) በኑፋቄ ወይም በክኅደት ትምህርት እንዳትጠመድ
2) ራስህን በትክክል ማወቅ ግልጽነትና ታማኝነት ያስፈልጋል
3) ራስህን በሌሎች ምዕመን ዓይን ለማየት መሞከር
4) በራስህ ዓይኖች በተጨባጭ ራስህን ተመልከት
5) ራስህን በሌሎች ሰዎች ወይም ምዕመን ቦታ አስቀምጥ