Thursday, March 22, 2012

በቤቱ ሳለህ የእግዚአብሔርን ውለታ አለመርሳት

በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!

በቤቱ ሳለህ የእግዚአብሔርን ውለታ አለመርሳት

አዕምሮ ያላቸው ፍጡራን ሰዎች በእያንዳንዱ ኹኔታ ያሉትን አያሌ አማራጮችን የመመልክት ኃይል አላቸው፡፡ ፍጹም ኹኔታዎችን በማየት ፈንታ ተቃራኒ የኾኑትን ይፈልጋሉ፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ ግን እንዲህ በማለት ይናገራል "ወደ ሕይወት ልትገባ ብትወድ ትዕዛዛትን ጠብቅ" ይለናል ማቴ 19÷17፡፡ ነገር ግን በእግዚአብሔር ቤት ሳለህ ውለታውን ሳትረሳና ሳትወጣ ለመኖር ከፈለግኽ የሚከተሉትን ተጥቦች በጥልቀት መርምራቸው፡፡

1) በኑፋቄ ወይም በክኅደት ትምህርት እንዳትጠመድ

2) ራስህን በትክክል ማወቅ ግልጽነትና ታማኝነት ያስፈልጋል

3) ራስህን በሌሎች ምዕመን ዓይን ለማየት መሞከር

4) በራስህ ዓይኖች በተጨባጭ ራስህን ተመልከት

5) ራስህን በሌሎች ሰዎች ወይም ምዕመን ቦታ አስቀምጥ

የሳባና የዓረብ ነገሥታት እጅ መንሻን ያመጣሉ ፤ የምድርም ነገሥታት ኹሉ ይሰግዱለታል

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን

“የሳባና የዓረብ ነገሥታት እጅ መንሻን ያመጣሉ ፤ የምድርም ነገሥታት ኹሉ ይሰግዱለታል” መዝ.71÷10-11


እነኾ የጥበብ ሰዎች /ሰብአ ሰገል/ ከሩቅ ምሥራቅ ወደ ኢየሩሳሌም ቤተልሔም አውራጃ መጡ፡፡ ከጥንት ዠምሮ በዓለም ሕዝብ መካከል ከዋክብትን የሚመረምሩ ጠቢባን ነበሩ፡፡ ትን.ዳን.1÷3 ስለነዚኽ ሦስት የሩቅ ምሥራቅ ነገሥታት አመጣጥ በስፋትና በጥልቀት በመዝ.71÷9-15 ኢሳ.60÷6 ኢሳ 49÷23፡፡ መመልከት ይቻላል፡፡

የጥበብ ሰዎች ስማቸው በድርሳነ ማርያም ላይ ተገልጧል፡፡ ታኔሱራም፣መሊክ፣ ዲሰስባ ወይም በትርጓሜ ወንጌል ላይ እንደተገለጸልን ማንቲሱራ፣መሊኩ፣በዲዳዝፋር በማለት ይጠራቸዋል፡፡

ከምሥራቅ የተነሡት ሰብአ ሰገል በምሥራቅ በኩል ያዩት ኮከብ ሕፃኑ ባለበት ላይ መጥቶ እስኪቆም ድረስ ይመራቸው ነበር፡፡ ለልማዱ ከሰው ሊደርሱ ይሰወራቸው ከሰው ሲለዩ ይመራቸው ነበር፡፡ መርቶ ከየት ያደርሰን ይኾን ብለው ኹለት ዓመት የተከተሉት ኮከብ ካሰቡት ቢያደርሳቸው ሕፃኑን አይተው ፈጽመው ደስ አላቸው፡፡ ምሥራቅ እመቤታችን ስትኾን ኮከብ ደግሞ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው፡፡ በትንቢትም ከያዕቆብ ይወጣል የተባለ ኮከብ እርሱ ነው፡፡ ዘኁ. 24 ÷17 እርሱም የሚያበራ የንጋት ኮከብ ነኝ ብሏል፡፡ ራእ.22÷16 ነገሥታቱም በኮከብ ተመርተው ቤቱን /የከብቶቹን ግርግም/ ባገኙ ሰዓት ሕፃኑን ከእናቱ ጋር ባዩዎቸው ጊዜ በጣም ደስ አላቸው ሳጥኖቻቸውንም ከፍተው እጅ መንሻ ወርቅ ፣ ዕጣንና ከርቤን አቀረቡለት፡፡

ለመለኮት በሚገባ ልደት ተወለደ

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱሰ አሐዱ አምላክ አሜን!
̒ ተወልደ በተድላ መለኮት - ለመለኮት በሚገባ ልደት ተወለደ ̕ቅዱስ ቄርሎስ
በትንቢት የተነገረለት የሰው  ልጆች ጥንተ ተፈጥሮ የፈጠረ የእግዚአብሔር ልጅ አኹን ደግሞ  ሰውን ለማዳን ሰው ኹኖ የተወለደበት ዕለት ነው፡፡  ልደት በየዓመቱ የሚከበረው ታኀሣሥ 29 ቀን ነው፡፡  በዘመነ ዬሐንስ ወንጌላዊ ግን / የሉቃስ ዘመን ጳጉሜን ስድስት ቀናት ስለኾነች ልደት ታኀሣሥ 28 ቀን ይሆናል፡፡  ይኽውም በዓል በሀገራችን በኢትዩጵያ መከበር የተዥመረው በዐፄ ዓምደ ጽዬን ዘመነ መንግስት  በ1 ሺ298ዓ.ም ነው ይባላል፡፡
የጌታ ልደት እንዴት ነበር?
እመቤታችን  ቅድስት ድንግል ማርያም የመውለጃዋ ወራት በደረሰ ግዜ ዓለሙ ኹሉ አንዲጻፍ/አንዲቆጠር / በንጉሥ አውግስጦስ ቄሣር ዘመነ መንግሥት በሮማ ነጉሠ ነገሥት ውስጥ የነበሩት ኹሉ በየትውልድ አውራጃቸወ እየኄዱ አንዲቆጠሩ በወጣላቸው ትዕዛዝ መሠረት ለመጻፍ /ለመቆጠር/  ከጠባቂዋና ከዘመዷ  ከዬሴፍ ጋር ከሰሜናዊው ገሊላ ከናዝሬት ከተማ ተነሥታ ወደ ደቡቧ ይሁዳ ቤቴልሔም ወደ ምትባል ወደ ዳዊት ከተማ ተጓዘች፡፡

ወነአምን በአሐቲ ጥምቀት ለስርየተ ኀጢአት

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን

ወነአምን በአሐቲ ጥምቀት ለስርየተ ኀጢአት - ኀጢአትን ለማስተሰረይ በምንጠመቃት በአንዲት ጥምቀት እናምናለን፡፡ 
ሃይማኖተ አበው ዘሠለስቱ ምእት

እንደ ናዝራውያን ሥርዓት በሦስትነት በምናመሰግነው እንደ ሱራፌልም ቃል በምናመሰግነው የሰው እጅ በማይነካው የሟችም ኀሊና በማይመረምረው በጽርሐ አርያም አትሮንሱን ያኖረ በተራሮች ራስ ላይ የጉምንተን በሚያተን ያለጩኸት የሚያስወግደው በአየራት ውስጥ በሚያመላልሰው ሰፊውን የሰማይ ገጽ የደመና ግምጃን በሚያላብሰው በእግዚአብሔር ስም ክብርና መመስገን የሚገባው ለዘላለሙ አሜን፡-

ጥምቀት ማለት በምስጢረ ሥላሴና በምስጢረ ሥጋዌ ለሚያምን ሰው ኹሉ የተሰጠ የኃጢአት መደምሰሻና ከእግዚአብሔር የጸጋ ልደትን መቀበየ ነው፡፡ ጥምቀት የኃጢአት መደምሰሻ እንደሚኾንም እግዚአብሔር አስቀድሞ በነቢያት ትንቢት አናግሮ ትንቢቱም በትንቢተ ሕዝቅኤል ላይ ……. የጠራ ውሃ አፈስባችኋለሁ ትጠሩማለችሁ ከርኩሰታችሁም ሁሉ አነጻችኋለሁ፡፡ በማለት ተናግሯል፡፡ ሕዝ . 36÷25 በመቀጠልም መልሶ ይምረናልኃጢአታችንንም ያጠፋል ኃጢአታቸው ኹሉ ወደ ጥልቅ ባሕር ትጥላለኽ ማለት ኃጢአታቸውን በጥምቀ ታስተሰርያለህ……./ትደመስሳለህ/ ሚክ. 7÷19

ምሥጢረ ሥላሴ

በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሓዱ አምላክ አሜን

ሥላሴ ጥንትና ፍጻሜ በሌለው ዘመን በአንድነት በሦስትነት ሲመሰገኑ ይኖራሉ፡፡ንባርኮ ለአብ ወልድ ወመንፈስ ቅዱስ እናዳሉ ሠለስቱ ደቂቅ ንባርኮ ብለው አንድነታቸውን አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ ብለው ሦስትነታቸውን ስቡሕኒ ውእቱ ወልዑልኒ ውእቱ ለዓለም ጥለው ጥንትና ፍጻሜ የሌላቸው መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ይሤለሱ በአካላት ወይትወሀዱ በመለኮት - በአካል ሦስት በመለኮት አንድ ይኾናሉ፤ እንዳለ ዮሓንስ ዘአንጾኪያ ተናግሯል፡፡ ሥላሴ አንድ ሲኾኑ ሦስት፤ሦስት ሲኾኑ አንድ ናቸው፡፡ ከሃይማኖት የወጡ የሰባልዮስ ወገኖች እንደሚሉት አንድ አካል አይባሉም፤በሦስቱ አካላት አንድ መለኮት አለ ይባላል እንጂ፤እንዳለ ባስልዮስ ዘቂሳርያ፡፡ ሥላሴ በተዋሕዶ ወተዋህዶ በሥላሴ ተጋብኦ በተከፍሎ ወተከፍሎ በተጋብኦ ሱስንዮስ እንደተናገረ፡፡
ቅድስት ሥላሴ የማይቀዳደሙ መሆናቸውን ቅድስት ቤተክርስቲያናችን እንደምታስተምረን ከሆነ ሰውና ፀሐይ ፤ እሳትና ውሃ ናቸው በማለት ታስተምራለች፡፡ሥላሴ አዳምን ' ንግበር ሰብኣ በአርአያነ ወበአምሳሊነ- ሰውን በመልካችን እንደምሳሌያችን እንፍጠር ' ዘፍ.1÷26 ብለው በፈጠሩት ጊዜ ተገኘ እንጂ አንዱ ቀድሞ ወደኃላ የተገኘ የለም ሥላሴም ኣብ ሳይቀድም ወልድን መንፈስ ቅዱስን አስገኘ፡፡ ወልድም ሳይከተል ከኣብ ተወለደ መንፈስ ቅዱስም ተለይቶ ሳይቀር ከኣብ ሠረፀ አብ አባት ነኝ ብሎ አልቀደመም፡፡ ወልድም ልጅ ነኝ ብሎ አልተከተለም መንፈስ ቅዱስም ሠራፂ ነኝ ብሎ አልቀረም፡፡ ኢሀሎ አብ አሓተ ሰዓተ- አብ ያለወልድና ያለመንፈስ ቅዱስ የነበረበት ጊዜ የለም፡፡ወልድም ያለ አብና ያለ መንፈስ ቅዱስ የነበረበት ጊዜ የለም፡፡ መንፈስ ቅዱስም ያለ አብና ያለወልድ የነበረበት ጊዜ የለም እናዳለ ሳዊሮስ